የአማራ ሴቶች ማህበር እና የኖርዌዥያን ፒፕል ኤድ (Norwegian people’s Aid) የስራ ቡድን ስርአተ-ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃትን መከላከልና ምላሽ መስጠት ተግባራት ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውይይት አካሄዱ።
የኖርዌዥያን ፒፕል ኤድ ቡድን ከማህበሩ የሀብት አፈላላጊ ኮሚቴ ጋር ባደረገው ውይይት፣ ማህበሩ በጥቃት መከላከልና ምላሽ መስጠት ረገድ ያለበትን የስራ ደረጃ ለመገምገም እና በቀጣይ በትብብር ለመስራት ያለውን ሁኔታ ለማወቅ ውይይት አድርጓል።
በማህበሩ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ገነት ወንድሙ በሚመራው የሀብት አፈላላጊ ቡድን ጋር በተደረገው ጥልቅ ውይይት፣ የማህበሩ ተቋማዊ አሰራር እና መዋቅራዊ አደረጃጀት ለወደፊት የጋራ ስራዎች አመቺ መሆኑን የኖርዌጂያን ፒፕል ኤድ የስራ ቡድን አባላት ገልጸዋል።




